በኪችነር ቤቴል የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን ሁለት ተጨማሪ መጋቢዎችን ሾመች፡፡ Bethel Ethiopian Evangelical Church in Kitchener appointed two pastors

ሴፕቴምበር 16 ቀን 2023 ዓመተ ምሕረት በተደረገው የደመቀ ስነ ስርዓት ላይ ቤተክርስቲያኗ በውስጧ እያገለገሉ ከነበሩ ቅዱሳን መካከል ወንድም ጥሩ ሰው ወልደየስንና ወንድም በፈቃዱ በመጋቢነት የሾመች ሲሆን የአገልግሎት ምደባቸውንም አሳውቃለች፡፡ በዕለቱ በተደረገው መንፈሳዊ የሹመት ስነ ስርዓት የቤተክርስቲያኗ ምዕመናን ፣ ከካናዳ የተለያዩ ከተሞች የመጡ በርካታ ቅዱሳን ፣ የኢትዮጵያና የኤርትራ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት መጋቢዎች ፣ ዘማሪዎችና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡
በዕለቱ የመጋቢዎችን ቃል የመግባትና የሹመት ስርዓት ያስፈጸሙት የቤተክርስቲያኗ ዋና መጋቢ ፓስተር መስፍን ብርሃኑ ሲሆኑ ለተሿሚዎቹ የተዘጋጀውን የምስክር ወረቀት የሰጡት ደግሞ ፓስተር ዮሐንስ ተፈራ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ከርሰቲያናት ሕብረት ዋና ጸሐፊ ናቸው፡፡
On September 16, 2023, Bethel Ethiopian Evangelical Church in Kitchener appointed two pastors among the saints who were serving in the church for a long time with a specified responsibility. In the Pastoral ordination ceremony held that day , the parishioners of the Church, Many Pastors, Gospel singers and ministers of the evangelical churches of Ethiopia and Eritrea were present.
Pastor Mesfen Berhanu, the Lead Pastor of the church, performed the Ordination process of the appointment ceremony of the pastors, followed by Pastor Yohannes Teffera, the general secretary of the Ethiopian Evangelical Churches Fellowship in Canada who distributed the certificate to the appointees.